ከቀጣይ ሣምንት ጀምሮ ከ14 ሚልየን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት በመላ ሀገሪቱ እንደሚሠራጭ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) አስታወቁ፡፡በአዳማ ጉምሩክ ጣቢያ የተለያዩ መሰረታዊ ሸቀጦችን ጭነው የቆሙ ከ700 በላይ ተሽከርካሪዎች ዛሬ የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት ሕግ መጨረሳቸውንም ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡ምርቱ ለገበያው በሚቀርብበት ሁኔታ ላይ በመወያየት የመፍትሔ አቅጣጫ መቀመጡንም ጠቁመዋል፡፡በዚህም መሠረት የገበያ ሁኔታን በዘላቂነት ለማረጋጋጥ በመንግሥት ወጭ የተገዛው ከ14 ሚልየን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት በሚቀጥለው ሣምንት በመላ ሀገሪቱ ይሠራጫል ብለዋል፡፡ 468
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።