“ጴጥሮስ ያቺን ሰዓት” በተሰኘው፥ በሎሬት ጸጋዬ ገ/መድኅን ቲያትር ላይ፥ ግርሻ የተሰኘ የዘመኑን አጎብዳጆች እሚወክል ገጸባህርይ አለ። “ለጥልያን እጅ እንስጥ” እሚልበት አመክንዮ የዋዛ እሚባል አይደለም። ለአቡነ ጴጥሮስ የኢትዮጵያን ፍጹም ሞት እሚያትትበት መንገድ አጀብ ነው። በቃላት አሽሞንሙኖ “ኢትዮጵያ ሞታለች” ብሎ ሊያረዳቸው ይባትላል። አቡነ ጴጥሮስ ኢትዮጵያን ከድተው በፋሽስት እንዲጠመቁ ሲያብል። አቡኑም እንዲህ ይሉታል፦ “እኔ በኢትዮጵያ ስለማምን፥ እኔ እስካመንኩ እሷ አትሞትም።”
አቡነ ጴጥሮስ የዛሬ 88 ዓመት ነበር ሰማዕትነትን የተቀበሉት!
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ