ሰራዊቱ ከሚሰጠው ሀገራዊ ግዳጅ በተጨማሪ መሰል ሀገራዊ እንቅስቃሴ ላይ አሻራውን እንደሚያሳርፍ እና በሀገሪቱ የልማት ተሳትፎ ላይ የበኩሉን አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ገለፁ። የኢፌዴሪ አየር ኃይል በዛሬው እለት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እያከናወነ ይገኛል። በዚህ ወቅት የአየር ሃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ፤ ሰራዊቱ በሀገሪቱ የልማት ተሳትፎ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በተለይም በአረንጓዴ አሻራ ሰፊ ስራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። የሚተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ ረገድ አየር ኃይሉ በትኩረት ይሰራል ያሉት ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ፤ ሰራዊቱ ከሚሰጠው ሀገራዊ ግዳጅ በተጨማሪ መሰል ሀገራዊ እንቅስቃሴ ላይ አሻራውን ያሳርፋል ብለዋል። አየር ኃይሉ እንደተቋም በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 25 ሺ ችግኞችን ለመትከል እንደሚሰራ የተገለፀ ሲሆን፤ በዛሬው መርሃ ግብር 10 ሺህ የቡና ችግኞች ጨምሮ የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች እየተተከሉ እንደሚገኝ ተጠቅሷል።
EBC
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ