ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ “የምትተክል ሀገር፣ የሚያጸና ትውልድ” በሚል መሪ ሃሳብ የጀመርነውን የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በጋምቤላ ክልል አስቀጥለናል ብለዋል፡፡መርሐ ግብሩን ዛሬ በጋምቤላ ክልል በአኙዋሃ ዞን በዲማ ወረዳ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ማከናወናቸውንም ገልጸዋል፡፡ከዚህ ቀደም በዚህ መርሐ ግብር ዓለምን ያስደመመ ስኬት አስመዝግበናል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ለዚህ ድል ደግሞ መንግስት እና ህብረተሰቡ በጋራ ያደረጉት ርብርብና ቁርጠኝነት ወሳኝ ነበር ነው ያሉት፡፡የአረንጓዴ ልማት በህብረተሰቡ ዘንድ ባህል ሆኖ እንዲቀጥል እና ለሌሎች ስራዎች እንደማስፈንጠሪያነት ያገለግል ዘንድ ሁሉም ባለድርሻ አካል ሚናውን እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
Al-Ain
More Stories
የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የማሻ ቅርንጫፍ ጣቢያ በመምህር ዳኪቶ ጋወቶ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማዉን ጥልቅ ሀዘን ገለፀ።
ማንቼስተር ዩናይትድ አርሰናልን በገዛ ሜዳው አሸነፈ
መልካም አብነቶች በማስፋት ወደ ብልጽግና የሚደረገውን ጉዞ እናፋጥናለን – ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)