ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ “የምትተክል ሀገር፣ የሚያጸና ትውልድ” በሚል መሪ ሃሳብ የጀመርነውን የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በጋምቤላ ክልል አስቀጥለናል ብለዋል፡፡መርሐ ግብሩን ዛሬ በጋምቤላ ክልል በአኙዋሃ ዞን በዲማ ወረዳ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ማከናወናቸውንም ገልጸዋል፡፡ከዚህ ቀደም በዚህ መርሐ ግብር ዓለምን ያስደመመ ስኬት አስመዝግበናል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ለዚህ ድል ደግሞ መንግስት እና ህብረተሰቡ በጋራ ያደረጉት ርብርብና ቁርጠኝነት ወሳኝ ነበር ነው ያሉት፡፡የአረንጓዴ ልማት በህብረተሰቡ ዘንድ ባህል ሆኖ እንዲቀጥል እና ለሌሎች ስራዎች እንደማስፈንጠሪያነት ያገለግል ዘንድ ሁሉም ባለድርሻ አካል ሚናውን እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
Al-Ain
More Stories
ከባድ የውንብድና እና የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል በእስራት ማስቀጣቱን የሸካ ዞን ፖሊስ አስታወቀ፡፡
በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሙስናን ለመከላከል በተደረገው ጥረት ከ85 ሚሊዮን በላይ ብር የህዝብ ሃብት ማዳን ተችላል
ኢትዮጵያ እና ኢንግሊዝ በኢንቨስትመንት፣ በንግድ እና ኢኮኖሚ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ ተስማሙ