የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በአዲስ አበባ የተጠናቀቁ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ በምክር ቤቱ የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) የተመራ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለምክር ቤቱ አባላት ገለፃ በማድረግ አስጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ከፒያሳ አራት ኪሎ እና ከሜክሲኮ ሣር ቤት የተጠናቀቁ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች ምልከታ ተደርጎባቸዋል። የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ ፕሮጀክቱ የአፍሪካ መዲና የሆነችውን አዲስ አበባ እንደስሟ አዲስና ልዩ ከተማ እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል።
EBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።