የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ከኬንያ መንገድ እና ትራንስፖርት ካቢኔ ፀሃፊ ኪፕቹምባ ሞርኮሜን ጋር በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ በናይሮቢ ተወያይተዋል።በውይይታቸውም የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ጉዳዮች ላይ የተወያዩ ሲሆን፤ በተለይም ሁለቱን ሀገራት በመሰረተ ልማት ማስተሳሰር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል።በተጨማሪም በኢትዮጵያ እና በኬንያ መካከል የጋራ የንግድ እና የኢኮኖሚ ዕድገት ትብብርን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ማድረጋቸው ተገልጿል።በውይይቱ በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ጄነራል ባጫ ደበሌ መሳተፋቸውን ከትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።