አጠር ያሉ ጉዞዎች በመኪና፣ በአውቶቡስ እና በባቡር መደረጋቸው የተለመደ ነው።ዌስትሬይ እና ፓፓ ዌስትሬይ በሚባሉት የስኮትላንድ ደሴቶች መካከል የሚደረገው የአውሮፕላን ጉዞ የዓለማችን አጭሩ በረራ በመሆን ተመዝግቧል።በደሴቶቹ መካከል ያለው ርቀት 2.7 ኪሎ ሜትር ሲሆን፤ ነዋሪዎች ከአንዱ ደሴት ወደ ሌላው ለማምራት ሁለት አማራጮች እንዳሏቸው ተገልጿል።በጀልባ መጓዝ አንዱ አማራጭ ሲሆን፤ ሌላኛው እና በነዋሪዎቹ ተመራጭ የሆነው አነስ ባለ አውሮፕላን የአየር ጉዞ ማድረግ ነው።የአየር ላይ ጉዞው 2 ደቂቃን እንደሚፈጅ የተገለፀ ሲሆን፤ ጥሩ የአየር ሁኔታ ካለ ከዚያም ሊያንስ እንደሚችል ነው የተገለፀው።ከ17 እስከ 45 ዩሮ የሚያስከፍለው ይህ ጉዞ በክረምት ወቅት ብዙ ቱሪስቶችን እንደሚስተናግድም ተገልጿል።
የዓለማችን አጭሩ በረራ

More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።