አጠር ያሉ ጉዞዎች በመኪና፣ በአውቶቡስ እና በባቡር መደረጋቸው የተለመደ ነው።ዌስትሬይ እና ፓፓ ዌስትሬይ በሚባሉት የስኮትላንድ ደሴቶች መካከል የሚደረገው የአውሮፕላን ጉዞ የዓለማችን አጭሩ በረራ በመሆን ተመዝግቧል።በደሴቶቹ መካከል ያለው ርቀት 2.7 ኪሎ ሜትር ሲሆን፤ ነዋሪዎች ከአንዱ ደሴት ወደ ሌላው ለማምራት ሁለት አማራጮች እንዳሏቸው ተገልጿል።በጀልባ መጓዝ አንዱ አማራጭ ሲሆን፤ ሌላኛው እና በነዋሪዎቹ ተመራጭ የሆነው አነስ ባለ አውሮፕላን የአየር ጉዞ ማድረግ ነው።የአየር ላይ ጉዞው 2 ደቂቃን እንደሚፈጅ የተገለፀ ሲሆን፤ ጥሩ የአየር ሁኔታ ካለ ከዚያም ሊያንስ እንደሚችል ነው የተገለፀው።ከ17 እስከ 45 ዩሮ የሚያስከፍለው ይህ ጉዞ በክረምት ወቅት ብዙ ቱሪስቶችን እንደሚስተናግድም ተገልጿል።
የዓለማችን አጭሩ በረራ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።