ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር በንግድ እና ልማት ዘርፍ ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል ገለጸች፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከፊንላንድ የውጭ ንግድና ልማት ሚኒስትር ቪሌ ታቪዮ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷በሀገራቱ የሁለትዮሽ ግንኙነት እና ተያያዥ ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ በትኩረት መክረዋል፡፡
አምባሳደር ምስጋኑ÷ፊላንድ በኢትዮጵያ በተለይም በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ንቁ ተሳትፎ እንድታደርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ፊንላንድ ለኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ላደረገችው ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸውንም የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡
ቪሌ ታቪዮ በበኩላቸው÷ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር በንግድና ልማት ዘርፍ ያላትን ትብብር ይበልጥ እንደምታጠናክር ተናግረዋል፡፡
ሁለቱ ወገኖች በቅርቡ የኢትዮ-ፊላንድ የጋራ የፖለቲካ ምክክር መድረክ ለማካሄድ መስማማታቸውም ተገልጿል፡፡
FBC
More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መንግስት የሚዘረጋቸውን የተለያዩ ኢንሸቲቦችን ቀድሞና ፈጥኖ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተሻሉ አፈጻጸሞች መታየታቸው ተገለፀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ