የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦትስዋና የቱሪስት መዳረሻ ወደ ሆነችው ማኡን ከተማ በረራ ጀመረ።
በማስጀመሪያው መርሐ-ግብር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስጻሚ መስፍን ጣሰው ፣የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ሃላፊ ለማ ያዴቻ በኢትዮጵያ የቦትስዋና አምባሳደር ተብሌሎ አልፈርድ ቦአንግ ተገኝተዋል።
አቶ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት÷ አየር መንገዱ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ መዳረሻውን በየጊዜው እያሰፋ ይገኛል።
አየር መንገዱ አፍሪካንና አፍሪካዊያንን ለማስተሳሰር የያዘውን ውጥን ከግብ ለማድረስ በትጋት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።