March 23, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ትራምፕ በኢራን የኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ለመፈጸም ያስቀመጡትን የጊዜ ገደብ ወደ አምስት ቀናት አራዘሙ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን የኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ለመፈጸም ያስቀመጡትን የ48 ሰዓታት የጊዜ ገደብ ወደ አምስት ቀናት አራዘሙ።

ትራምፕ በመካከለኛው ምሥራቅ ስላለው ግጭት ከኢራን ጋር ሙሉ በሙሉ እና አጠቃላይ መፍትሔ መድረስን በተመለከተ ውይይቶች ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

ፕሬዚዳንቱ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መረጃ÷ በኢራን የኃይል ማመንጫዎች እና የኢነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚደረጉ ጥቃቶችን ለሌላ ጊዜ አስተላልፋለሁ ብለዋል።

ቴህራን የሆርሙዝ ወሽመጥን በ48 ሰዓታት ውስጥ ካልከፈተች የኃይል ማመንጫዎቿን ለማጥቃት የገለጹ ቢሆንም አሁን ግን ለመጪዎቹ አምስት ቀናት ርምጃቸውን እንዳዘገዩ አመላክተዋል።

ትራምፕ ከኢራን ጋር ባለፉት ሁለት ቀናት በመካከለኛው ምሥራቅ አለመረጋጋት ዙሪያ በጣም ጥሩና ውጤታማ ንግግር አድርገናል ማለታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

በዚህም የሀገራቸው ጦር በኢራን የኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት እንዳይፈጽም ማዘዛቸውን ገልጸው÷ ጥቃቱን ለአምስት ቀናት እንደሚያዘገዩና ቀጣይ ውሳኔያቸው እየተካሄደ ባለው ንግግር ላይ እንደሚመሰረት አስታውቀዋል።