በሸካ ዞን በሁሉም መዋቅሮች የፓርቲና የመንግስት ሥራዎች አፈጻጸም የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮች አካላት በተገኙበት በቴፒ ከተማ እየተገመገመ ይገኛል።
የፓርቲና የመንግስት ኢንሼቲቮችን በበላይነት በመምራትና ውጤታማነታቸው ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥሉ አመራሩ በባለቤትነት በመምራት የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንዲያስችል የጋራ መግባባት ላይ እንዲደረስ ያለመ የውይይት መድረክ እንደሆነም ተጠቁሟል።
በወረዳና በከተማ አስተዳደር የተደረጉ የአመራር ግምገማና ምዘና አፈጻጸም እየተገመገመ ይገኛል።
የአመራር ምዘናው ጠንካራ ተቋም በመገንባት የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚረዳና አሰራሮችን በመትከልና የፓርቲውን ተልዕኮዎች በብቃት በመፈጸም ውጤታማ አሰራር እንዲኖር ማስቻል ዓላማው እንደሆነም ተገልጿል።
በውይይቱ አመራሩ ለቀጣይ ተልእኮ ራሱን የሚያዘጋጅ እና ለህዝቡ የላቀ ተጠቃሚነት ተግባራትን የሚመራበት አቅጣጫም የሚቀመጥ ይሆናል።
በመድረኩ የክልል ደጋፊ አመራሮች፣የዞን ማዕከል አጠቃላይ አመራሮችና የወረዳ/ከተማ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት እየተሳተፉ ይገኛሉ ሲል የዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።
More Stories
አሜሪካ ለኢራን ፍልሚያ ተጨማሪ 200 ቢሊዮን ዶላር ጠየቀች!
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮምሽነር ዶክተር ካሳ ለ1,447ኛዉ ለኢድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ለ1,447ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ