የሸካ ዞን ምክር ቤት እያካሄደ ባለው 5ኛ ዙር፣ 13ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 24ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ በጤናው ዘርፍ የተከናወኑ ሪፖርት ለምክር ቤቱ ቀርቧል ።
በጉባኤው ላይ የአስፈጻሚ አካላትን የ2018 ዓ.ም የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ በዞኑ ለጤና ስጋት ከሆኑ በሽታዎች መካከል የወባ በሽታ ወረርሽኝ አንዱ እንደሆነ ተመላክቷል ።
በዚህም በ2018 በጀት ዓ.ም 6ወራት ውስጥ 58ሺ 8መቶ 39 ሰዎች የወባ በሽታ ተገኝቶባቸው የህክምና አገልግሎት መሰጠት መቻሉን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገልፀዋል ።
የበሽታውን ስርጭት ለመከላከል ከጤና ሚናስቴር የቀረቡ 21 ሺ 8መቶ አጎበሮችን ለ9ሺ 99 አባወራዎች እና እማወራዎች ማሰራጨት መቻሉን ዋና አስተዳሪው ጠቁመዋል ።
በሽታውን ለመከላከል ክትባት የመስጠት እና የኬሚካል ርጭት ስራዎች በስፋት በመሰራታቸው የስርጭት መጠኑ እየቀነሰ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የጤና መድህን ስራን በተመለከተ 34 ሺ 55 የመዐጤመ አባል አባወራ እና እማወራ ውስጥ 92 ሺ 65 አባላት በድግግሞሽ የህክምና አገልግሎት እንዳገኙ ተገልጿል ።
More Stories
አሜሪካ ለኢራን ፍልሚያ ተጨማሪ 200 ቢሊዮን ዶላር ጠየቀች!
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮምሽነር ዶክተር ካሳ ለ1,447ኛዉ ለኢድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በሸካ ዞን የፓርቲና የልማት ስራዎች አፈጻጸም እየተገመገመ ነዉ