February 4, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ማንቼስተር ዩናይትድ አርሰናልን በገዛ ሜዳው አሸነፈ

ማሻ፤ ጥር 18/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በ23ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ማንቼስተር ዩናይትድ አርሰናልን 3 ለ 2  አሸንፏል።

የማንቼስተር ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች ምቤሞ፣ ዶርጉ እና ኩንያ ከመረብ አሳርፈዋል።

ምሽት 1፡30 በኢምሬትስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የአርሰናልን ግቦች ማርቲኔዝ (በራስ ላይ) እና ሜሪኖ አስቆጥረዋል።

በዚህም ማንቸስተር ዩናይትድ በዚህ የውድድር ዘመን አርሰናልን በገዛ ሜዳው ያሸነፈ የመጀመሪያው ቡድን ሆኗል።