ማሻ፤ ጥር 15/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመስተዳድር ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 46ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል ፡፡
በዚህም መሠረት፦
1ኛ.የቀረቡ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎች ላይ ተወያይቷል። በዚህም የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን በግብርና 27፣ በኢንዱስትሪ 4 እና በአገልግሎት 2 በአጠቃላይ 1.4 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ጥያቄዎችን መርምሮ ወደ ስራ እንዲገቡ ወስኗል።
2ኛ. መስተዳድሩ ምክር ቤቱ የገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ወደ ምክር ቤት መርቷል። እንዲሁም የታክስ አስተዳደር ደንብ መርምሮ አጽድቋል።
3ኛ. መስተዳድር ምክር ቤቱ የገጠር ኮሪደር ሥራዎች ዙሪያ ተወያይቶ አቅጣጫ ማስቀመጡን ከክልሉ መ/ኮ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።