ማሻ፣ ጥር 07/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) የአክስቱን ልጅ የአስር ዓመቷን ታዳጊ ላይ የግብረስጋ ድፍረት ወንጀል የፈፀመ ግለሰብ በ25 ዓመት ፅኑ እስራት መቅጣቱን የማሻ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍረድ ቤት አስታወቀ፡፡
የማሻ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዛሬ ማለትም ተከሳሽ ዋስሁን እምሩ የእስራት ቅጣቱ ሊወሰንበት የቻለው የአስር ዓመቷን ታዳጊ ላይ የግብረስጋ ድፍረት ወንጀል በመፈጠሙና ጥፋተኝነቱ በማስረጃ በመረጋገጡ ነው፡፡
ተከሳሽ ዋስሁን እምሩ ህዳር 22 ቀን 2018 ዓ.ም በማሻ ከተማ አስተዳደር ከለበሪ መንደር የግል ተበዳይ ዕድሜ 10 ዓመት የሆነችውን የአክስቱን ልጅ አብረው የዘመድ ቤት ጠብቀው እንዲያድሩ ተደርጎ ከጮህሽ እገልሻለሁ ብሎ በስለት በማስፈራራት እና ራሷን መከላከል እንዳትችል በማድረግ በኃይል የግብረስጋ ድፍረት ወንጀል መፈፀሙን ፖሊስ በህክምና ማስረጃ እና ተበዳይ በሰጠችው ቃል በማደራጀት መዝገቡን ለዐቃቤ ህግ ይልካል፡፡
ዐቃቤ ህግ ከፖሊስ የደረሰውን የምርመራ መዝገብ መነሻ በማድረግ ግለሰቡን የኢፌዴሪ ወንጀል አንቀጽ 627 (1) ሥር የተመለከተውን በመተላለፍ በህጻናት ልጆች ላይ የሚፈጸም የግብረስጋ ድፍረትበደል ወንጀል ክስ መስርቶበት ፍርድ ቤት አቅርቦታል፡፡
የማሻ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከዐቃቤ ህግ የቀረበለትን የክስ መዝገብ ግራ ቀኙን ሲያከራክር ቆይቶ ተከሳሹ በዐቃቤ ህግ የቀረበበትን በህጻናት ልጆች ላይ የሚፈጸም የግብረስጋ ድፍረት በደል ወንጀል ክስ መከላከል ባለመቻሉ ጥፋተኛ ነው ሲል የጥፋተኝነት ብይን ሰጥቷል፡፡
ተከሳሽ ወንጀሉን የፈፀመው በክህደት፣በወራዳነት ፍፁም ፍቃደኛ በመሆን በተለየ ከፍተኛ ጭካኔ በተሞላበት እንዲሁም ተከሳሹ ከግል ተበዳይ ህፃን ሴት ልጅ ጋር ዘመድ በመሆኑ አብረው የዘመድ ቤት ጠብቀው እንዲያድሩ የተጣለውን እምነት ወደ ጉን በመተው ወንጀሉን የፈፀመ በመሆኑእና ቀደም ሲል በስርቆት ወንጀል ተከሶ የተቀጣ እንደሆነ የጠቀሰው ዐቃቤ ህግ ተከሳሽ ወንጀሉን የፈፀመው መከላከል በማትችለው ታዳጊ ልጅ ላይ በመሆኑ ፍርድ ቤቱ በተከሳሹ ላይ ቅጣቱን አክብዶ እንዲወስን ዐቃቤ ህግ ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡
ፍርድ ቤቱ ከሳሽ ዐቃቤ ህግ የሰጠውን ቅጣት ማክበጃ ምክንያቶችን የኢፌዴሪ ወንጀል ህግ አንቀጽ 84(1) ሀ፣ለ፣ሐ፣ሠ ሥር የተመለከቱትን በድምሩ4 ቅጣት ማክበጃ ምክንያቶችን ተቀብሏል፡፡
በዚህ መሰረት የማሻ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍረድ ቤት ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሽ እና መሰል ወንጀል አድራጊዎችን ያስተምራል፤ሌሎችን ያስጠነቅቃል በሚል ተከሳሽ ዋስሁን እምሩ 25 አመት ፅኑ እስራት እንድቀጣ ፍርድ ቤቱ እንደተወሰነበት የማሻ ከተማ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ጠቅሶ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን ዘግቧል
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።