February 4, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ማንቼስተር ሲቲ እና ቼልሲ አቻ ተለያዩ

ማሻ፣ ታህሳስ 27/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) በ20ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ እና ቼልሲ 1 አቻ ተለያይተዋል።

የማንቼስተር ሲቲን ግብ ቲጃኒ ሬንደርስ ሲያስቆጥር ለቼልሲ ደግሞ ኢንዞ ፈርናንዴዝ ከመረብ አሳርፏል።

አስቀድሞ በተደረጉ ጨዋታዎች ሊቨርፑል ከፉልሃም ሁለት አቻ ፣ማንቼስተር ዩናይትድ ከሊድስ ዩናይትድ እንዲሁም ቶተንሃም ሆትስፐር ከሰንደርላንድ በተመሳሳይ አንድ አቻ ተለያይተዋል፡፡

በሌላ የሊጉ ጨዋታዎች ኒውካስል ዩናይትድ ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 0 እንዲሁም ብሬንትፎርድ ኤቨርተንን 4 ለ 2 በሆነ ውጤት ማሸነፋቸው ይታወቃል፡፡