February 4, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ሱዳን ኢኳቶሪያል ጊኒን አሸነፈች

ማሻ፣ ታህሳስ 19/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ሁለተኛ ዙር ጨዋታ ሱዳን ኢኳቶሪያል ጊኒን 1 ለ 0 አሸንፋለች።

በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ምሽት 12፡00 ላይ በተደረገው ጨዋታ የሱዳንን የማሸነፊያ ግብ ሳውል ኮኮ በራሱ መረብ ላይ አሳርፏል።

ቀደም ሲል ቀን 9፡30 ላይ በተደረገው ጨዋታ ሞዛንቢክ ጋቦንን 3 ለ 2 ማሸነፍ ችላለች።

የዕለቱ መርሐ ግብር ቀጥለው ሲካሄዱ ምሽት 2:30 ላይ አልጄሪያ ከቡርኪናፋሶ፤ ምሽት 5 ሰዓት ኮቲዲቯር ከካሜሩን ይጫወታሉ።