ማሻ፣ ታህሳስ 19/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ሁለተኛ ዙር ጨዋታ ሱዳን ኢኳቶሪያል ጊኒን 1 ለ 0 አሸንፋለች።
በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ምሽት 12፡00 ላይ በተደረገው ጨዋታ የሱዳንን የማሸነፊያ ግብ ሳውል ኮኮ በራሱ መረብ ላይ አሳርፏል።
ቀደም ሲል ቀን 9፡30 ላይ በተደረገው ጨዋታ ሞዛንቢክ ጋቦንን 3 ለ 2 ማሸነፍ ችላለች።
የዕለቱ መርሐ ግብር ቀጥለው ሲካሄዱ ምሽት 2:30 ላይ አልጄሪያ ከቡርኪናፋሶ፤ ምሽት 5 ሰዓት ኮቲዲቯር ከካሜሩን ይጫወታሉ።
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ