ማሻ፣ ታህሳስ 17/2018 (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ብጹዕ አቡነ ሕዝቅኤል የከፋ ሸካ ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ:የሰዋስው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ እና የሲኖዶስ አባል በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው ።
ብጹዕነታቸው በቆይታቸውም የሸካ ሀገረ ስብከትን በማቋቋም ለሀገረ ስብከት ጽ/ቤት እና መንበረ ጵጵስና ግንባታ መሠረተ ድንጋይ እንደሚያስቀሚጡ የሚጠበቅ ነው ።
ብጹዕ አቡነ ሕዝቅኤል የከፋ ሸካ ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ:የሰዋስው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ እና የሲኖዶስ አባልን ጨምሮ የሀገረ ስብከቱ ልዑክ ጋር በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል ።
በአቀባበል ስነ ስረዓቱ ላይ የየኪ ወረዳ ቤተኪህነት ፣ የአራቱ አድባራት አገልጋዮች ፣ ማህበረ ቅዱሳን የቴፒ ወረዳ ማዕከል፣ የማሻና የጌጫ አጥቢያ ቤተክርስቲያናት አገልጋዮችና የሰበካ ጉባኤ አባላትን ጨምሮ ሌሎች የሃይማኖት አባቶችና የእምነቱ ተከታዮች ታድመዋል ።
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።