ዶ/ር ደረጄ የወባ መከላከያ ክትባትና የአልጋ አጎበር ስርጭትን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን ቱርሚ ከተማ በመገኘት በይፋ አስጀምረዋል።
በወቅቱም በሽታን በ2030 ለማጥፋት እየተደረገ ባለው ርብርብ የጸረ ወባ ክትባት ዘመቻው ከፍተኛ እገዛ እንዳለው ገልጸው÷ ክትባቱ የወባ ስርጭት ባለባቸው 58 ወረዳዎች እንደሚካሄድ አመልክተዋል።
ክትባቱ በዓለም ጤና ድርጅት ውጤታማነቱ የተረጋገጠና አስተማማኝ መሆኑን አንስተው፥ ወላጆችና አሳዳጊዎች ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናትን በማስከተብ ግዴታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
ከዚህ በተጓዳኝ ከ3 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ የአልጋ አጎበሮች የወባ ጫና ላሉባቸው አካባቢዎች እንደሚሰራጩ መናገራቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …