ይህን ያለው የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ነው።
ኢንስቲትዩቱ በበጋው የአየር ሁኔታ በሚኖር ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በትግራይ፣ አማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ኦሮሚያ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ብሏል፡፡
ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት አከባቢዎች የዝናብ መቆራረጥ ሊኖር እንደሚችልም ተጠቁሟል።
ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት እንደ ቦረናና ጉጂ ዞኖች፣ ሲዳማ እና ደቡብ ኢትዮጵያ መደበኛ ዝናብ የሚኖራቸው መሆኑን ኢንስቲትዩቱ ተናግሯል።
የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍል ደግሞ ከመደበኛ በታች የሆነ የዝናብ መጠንና ስርጭት እንደሚያገኙ ተጠቁሟል።
በሌላ በኩል የምዕራብና ደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከመደበኛ በላይ ዝናብ እንደሚያገኙም ተነግሯል።
ኢንስቲትዩቱ ግንቦት ላይ የሰጠው የክረምት ወቅት የአየር ጠባይ ትንበያ መሬት ላይ ከተከሰተው ጋር የተጣጣመ እንደነበረም ተነግሯል፡፡
ማህበረሰቡ የደረሱ ሰብሎችን በወቅቱ እንዲሰብሰቡ ማድረግ ከመደበኛ በታች ዝናብ በሚስተዋልባቸው የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍል የሚገኘውን የዝናብ መጠንና ስርጭት በአግባቡ መጠቀም ያስፈልጋል ሲል ኢንስቲትዩቱ አሳስቧል ሲል የዘገበው ሸገር ኤፍ ኤም ነው።
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ በጋራ ስንቆም ከተራራ የገዘፍን ከብረት የጠነከርን ስለመሆናችን ህያው ምስክር ነዉ :-ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋገሾ