አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የህዳሴው ግድብ መጠናቀቅ ኢኮኖሚያዊ ትስስርን በማሳደግ ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሰላምን የሚያመጣ ነው አሉ ምሁራን።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባለፈው ሳምንት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቁንና በመጪው መስከረም ወር እንደሚመረቅ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡
የግድቡ መጠናቀቅ ኢኮኖሚያዊ ትስስርን በማሳደግ ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሰላምን የሚያመጣ መሆኑን ነው የፖለቲካና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁራን የሚገልጹት፡፡
የፖለቲካ ጉዳዮች ተንታኙ ሴኔሳ ደምሴ እንደሚሉት፥ የህዳሴው ግድብ ከፍ ያለ ኃይል የያዘ በመሆኑ ሰጥቶ የመቀበል አለምአቀፍ የዲፕሎማሲ መርህ ተግባራዊ እንዲሆን ለምስራቅ አፍሪካ ሰላም በር ከፋች ይሆናል።
አንዱ የሌለውን ከሌላው ጋር እንዲጋራው በማድረግ ምጣኔ ሀብታዊ ትስስርን በማሳደግ ቀጣናውን ወደ ሰላም የማምጣት ዕድል እንዳለው አንስተዋል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህሩ የእዮብዘር ዘውዴ በበኩላቸው፥ የግድቡ መጠናቀቅ የኢትዮጵያን ተጽዕኖ ከነበረበት ከፍ እንደሚያደርገው ተናግረዋል፡፡
ከዚህም ባለፈ ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ከፍ ያለ ጥቅም ይዞ እንደሚመጣ ነው የተናገሩት።
በክብረወሰን ኑሩ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።