December 17, 2025

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ቴፒ የምርት ጥራት ምርመራና ሰርቲፊኬሽን ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ተገለፀ።

ማሻ ፣ የሀምሌ 01፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) በኢፌዲሪ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ የምርት ጥራትና ሰርቲፊኬሽን ማዕከል የፌዴራልና ክልል ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተመርቋል ።

በምረቃው ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)፣ የኢፌዲሪ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የኢፌዲሪ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች ፣ የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች እንዲሁም የአከባቢው ማኅበረሰብ ተገኝተዋል።