ማሻ ፣ የሰኔ 25፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ኢትዮጵያ እየተጠናቀቀ ባለው የበጀት ዓመት ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ቶን በላይ የቡና ምርት ማግኘቷን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል።
ባለስልጣኑ ሕገ-ወጥ የቡና ንግድን መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከፌዴራልና ከክልሎች የፀጥታ፣ ከግብርናና ንግድ ዘርፎች ከተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል፡፡
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ የቡና ምርትን ከማሳደግ አንፃር በርካታ ስራዎችን እየተሰሩ በመሆኑ ውጤት ተገኝቷል።
በተጨማሪም ወደ ውጭ የሚላከውን የቡና ጥራት ይበልጥ ለማስጠበቅ ተጨማሪ አራት የቅምሻ ማዕከላት ለመክፈት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።
በዚህም የቡና ምርት በጥራትም ሆነ በብዛት በተሻለ ደረጃ ማደጉን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
የተገኘውን ስኬት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ሕገ-ወጥ የቡና ንግድና ዝውውር መግታት ላይ በትኩረት መስራት ይገባል ማለታቸውን የኢትዮጵያ ሬዲዮ ዘግቧል።
ባለፉት 11 ወራት 409 ሺህ ቶን ቡና ለውጭ ገበያ መቅረቡ የሚታወስ ነው።
ኢቢሲ
More Stories
ቴፒ የምርት ጥራት ምርመራና ሰርቲፊኬሽን ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ተገለፀ።
ከቡና ወጪ ንግድ ከ2 ነጥብ 24 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ
ለሀገሪቱ ዋነኛ የውጭ ምንዛሪ የሚያስገኝ ቡና እንደ ወረዳ ከ30 ሺህ ሄክታር በላይ ሽፋን መኖሩን በሸካ ዞን የየኪ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ።