August 21, 2025

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ትራምፕ ቲክ ቶክን የሚገዙ የአሜሪካ ባለሀብቶች ማግኘታቸውን ገለፁ

ማሻ ፣ የሰኔ 23፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፎክስ የዜና ጣብያ ጋር ባደረጉት ቆይታ የአጫጭር ቪዲዮ ማጋሪያ የሆነውን ቲክ ቶክ የሚገዙ ባለሀብቶች ማግኘታቸውን አስታዉቀዋል።

የገዢዎቹን ማንነት ከሁለት ሳምንት በኋላ ይፋ እንደሚያደርጉም ነው ፕሬዝዳንቱ የገለፁት።

ንግግሩ አሁን ላይ እየተደረገ መሆኑንና ከቻይና ፈቃድ እንደሚያስፈልግ የገለጹት ፕሬዝዳንት ትራምፕ፤ የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ያደረጉታል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ብለዋል።

ባለፈው ዓመት ባይትዳንስ የተሰኘው የቻይናው ኩባንያ የቲክቶክ መተግበሪያን ለአሜሪካዊ ባለሃብት የማይሸጥ ከሆነ እንዲዘጋ መወሰኑ ይታወሳል።

ሆኖም የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ስልጣን በመጡ ጊዜ ሊዘጋ የነበረውን ቲክ ቶክን በ3 ወር አራዝመው ለአሜሪካዊ ድርጅት እንዲሸጥ ጥሪ አቅርበው ነበር።

አሁን ላይ ገዢ እንደተገኘ እና ንግግር ላይ መሆናቸውን የገለፁት ፕሬዝዳንቱ፤ በሚቀጥሉት ሳምንታት የገዢዎቹን ማንነት በይፈ እንደሚያስታውቁ ጠቅሰዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ትራምፕ በቅርቡ ቲክቶክ ለተጨማሪ 90 ቀናት በሀገረ አሜሪካ እንዲሰራ መፍቀዳቸዉ የሚታወስ ነዉ።

ኢቢሲ