ማሻ ፣ የሰኔ 24፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በካፋ ዞን አውራዳ ከተማ አስተዳደር የተገነባውን የአውራዳ ኮንስተትራክሽ እና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ መርቀው ከፍተዋል።
ሙሉ በሙሉ የግንባታ ወጪው በክልሉ መንግሥት የተሸፈነው ኢንዱስትሪያል ኮሌጁ በውስጡ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ፥ ባሌ 2 ፎቅ የአስተደዳደር ህንፃ፤ባሌ 1 ፎቅ የመማርያ ክፍል፤ላይቢራር ፤1 የመሰብሰቢያ አዳራሽ ፤2 መጸዳጃ ቤቶች ወዘተ ያካተቴ ስሆን ግንባታዉን አሁን ባለዉ ደረጃ ለማጠናቀቅ 53 ሚሊዮን 845ሺህ 246 ብር ወጪ እንደወጣበት ነው የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ዐቢይ አንደሞ (ዶ/ር) የገለጹት።
በምረቃው ስነስርዓት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው፣ የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደን ጨምሮ የክልል እና የካፋ ዞን እንዲሁም የአውራዳ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የአከባቢው ማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
ክልል ኮሚኒኬሽን
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …