ማሻ ፣ የሰኔ 24፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) 6ኛው ዙር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 41ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው።
ምክር ቤቱ በስብሰባው በፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ በዝርዝር እየተወያየ ነው።
የገንዘብ ሚኒስቴሩ አሕመድ ሽዴ ከምክር ቤቱ አባላት የቀረቡ ጥያቄ እየተቀበሉ ሲሆን፤ የምክር ቤቱ አባላት የበጀት አቅርቦቱ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች ምን ያክል በቂ ነው የሚል ጥያቄ አቅርበዋል።
የበጀት ድልድሉ ፍትሃዊነት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን የሕዝብና የቤት ቆጠራ መደረግ እንዳለበት ተነስቷል።
በክልል የተለያዩ አካባቢዎች የመንገድና ጥገናና ፕሮጀክቶች ግንባታ ሊደረግ ይገባል የሚሉና የክልሎች የበጀት ድጎማ ከፍ ማለት አለበት የሚሉ ጥያቄዎችም ቀርበዋል።
የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እንደሚሰጡ ይጠበቃል።
ኢቢሲ
More Stories
ሚኒስቴሩ ለሦስት ኩባንያዎች የማዕድን ምርት ፍቃድ ሰጠ
በክልሉ ከሚገኙ ቡና አቅራቢ ነጋዴዎች ጋር በወቅታዊ የቡና ገበያ ላይ በቦንጋ ከተማ ምክክር እየተደረገ ነዉ
የጣሊያን ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያላቸውን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲያጠናከሩ ተጠየቀ፡፡