ምክር ቤቶች የህዝቡ ሁለተናዊ ተጠቃሚነት እንድረጋጥ ድርሻቸው የጎላ በመሆኑ የድጋፍና ክትትል ስራዎችን ማጠናከር እንደምያስፈልግ ተጠቆመ ።
ማሻ ፣ የሰኔ 06፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የየኪ ወረዳ ምክር ቤት 5ኛ ዙር 12ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤን በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
በዚህ ጉባኤ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የየኪ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ መላኩ ብዙነህ በወቅቱ እንደገለፁት ምክር ቤቶች የወከላቸውን ህዝብ ሁለተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች እንድፈቱ በማድረግ በኩል ድርሻቸው የጎላ እንደሆነ ተናግረዋል ።
በመሆኑም የወረዳው ህዝብ በኢኮኖሚ ፣ ማህበራዊና በተለያዩ ዘርፎች ተጠቃሚ እንድሆኑ ለማስቻል በየደረጃው ካሉ ምክር ቤቶች ጋር በመሆን ስሰራ መቆየቱን ጠቁመው የአካባቢውን የገቢ አቅም ባገናዘበ መልኩ ገቢን አሟጦ መሰብሰብ ያስፈልጋል ስሉ ጠቁመዋል ።
የአስፈጻሚ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ9ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳውት ተሰማ የቀረበ ሲሆን የባለፈውን ቃለ-ጉባኤን መርምሮ ማፅደቅን ጨምሮ አምስቱ የገጠር ቀበሌዎችን ወደ ከተማ መካለላቸውን መርምሮ ምክር ቤቱ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
በዚህ ጉባኤ ላይ የየኪ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ መላኩ ብዙነህ ፣ምክትል አፌ ጉባኤ ወ/ሮ ድርጀት ከበደ፣ የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዘጋቢ አስቻለው አየለ
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።