ማሻ ፣ የግንቦት 17፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ለመስጠት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን የትምህርት ፈተናና ምዘና አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ ተናገሩ።
አብዛኛውን ጊዜ ፈተና ሲነሳ የፈተና ስርቆትና ኩረጃ አብሮ የሚነሳ ሲሆን፤ ይህን ለማስቀረት መንግስት ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ የ12ኛ ክፍል ሀገረ አቀፍ ፈተናን ተማሪዎች ከተማሩበት ት/ቤት ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ገብተው እንዲፈተኑ አድርጓል።
ለፈተና ስረቆትና ኩረጃ የሚያግዙ ድምፅን ምስልን የሚወስዱ ማንኛውንም መሳሪያዎችን ተማሪዎች እንዳይጠቀሙና ይዘውም እንዳይገኙ በመከልከል፤ ጥብቅ ፈተሻ እንደሚደረገ የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ ተይዘው ሲገኙም እርምጃ እንደሚወሰድባቸው ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
ተማሪዎች ፈተናን ለመስረቅና ለመኮረጅ የሚያባክኑትን ጊዜ ትምህርቱን በሚገባ ቢያጠኑበት መልካም ነው፤ ውጤታማም ብለዋል።
በብይነ-መረብና በወረቀት የሚሰጠው የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በተሳካ መንገድ ለመስጠት፤ የትምህርት ተቋማት የቁሳቁስና የተለያዩ ዝግጅቶችን አጠናቀው ተማሪዎችን በመጠበቅ ላይ እንደሚገኙም ገልጸዋል።
ፈተናውን በብይነ መረብ የሚፈተኑ ተማሪዎች በየትምህርተ ቤታቸው ልምምድ በማድረግ ላይ እንዳሉ የጠቆሙት ዶ/ር እሸቱ፤ ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎችም ተገቢውን ግንዛቤ እንዲያገኙ እየተደረገም ይገኛል ነው ያሉት።
ፈተናው በስኬት እንዲጠናቀቅ ለፈተናው የሚያስፈልጉ ግብአቶች ዝግጁ መሆናቸውን መፈተሸና ለሰው ሀይል ስልጠናዎችን መስጠት፤ እንዲሁም ከክልል ትምህርት ቢሮ አመራሮችና ከዩኒቨርሲቲ የበላይ አመራሮች ጋር በቅርበት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ኢቢሲ
More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።
የሰው ተኮር ተግባራት በማጠናከር ሁለተናዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገለፁ።