ማሻ ፣ የግንቦት 20፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የኬንያ ህገ አውጪ ምክር ቤት የኢጋድን ስምምነት ማፅደቁን የምስራቅ አፍሪካ በየነ መንግሥታት የልማት ድርጅት (ኢጋድ) ዋና ፀሃፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) አድንቀዋል።
የኢጋድ ስምምነት በሀገሪቱ ምክር ቤቱ መፅደቁ ድንበር ዘለለ ተግዳሮቶችን በመከላከል ዘላቂ ሰላምንና ብልፅግናን ለማረጋገጥ ቀጠናዊ ትብብርና ለማጠናከር ያግዛል ብለዋል።
የቀጠናው ሀገራት በጋራ ጉዳይ ለመስራት ቁርጠኝነታቸውን የሚገልፁበት የኢጋድ ስምምነት ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ በጅቡቲ እና በደቡብ ሱዳን ህግ አወጪ አካላት መፅደቁ ይታወሳል።
በሀገራቱ መካከል ሰላማዊ ግንኙነትን ማረጋገጥ፣ ጤናማ ጉርብትና መፍጠር፣ በጎረቤት ሀገራት ጉዳይ ጣልቃ አለመግባት፣ በሀገራቱ መካከልም ሆነ በሀገራቱ ውስጥ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት፣ ቀጠናቂ ሰላምን መረጋጋት እንዲሁም ደህንነት ማረጋገጥ የኢጋድ ስምምነት ዋንኛ ዓላማዎች ናቸው ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።