ማሻ ፣ የግንቦት 20፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የኬንያ ህገ አውጪ ምክር ቤት የኢጋድን ስምምነት ማፅደቁን የምስራቅ አፍሪካ በየነ መንግሥታት የልማት ድርጅት (ኢጋድ) ዋና ፀሃፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) አድንቀዋል።
የኢጋድ ስምምነት በሀገሪቱ ምክር ቤቱ መፅደቁ ድንበር ዘለለ ተግዳሮቶችን በመከላከል ዘላቂ ሰላምንና ብልፅግናን ለማረጋገጥ ቀጠናዊ ትብብርና ለማጠናከር ያግዛል ብለዋል።
የቀጠናው ሀገራት በጋራ ጉዳይ ለመስራት ቁርጠኝነታቸውን የሚገልፁበት የኢጋድ ስምምነት ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ በጅቡቲ እና በደቡብ ሱዳን ህግ አወጪ አካላት መፅደቁ ይታወሳል።
በሀገራቱ መካከል ሰላማዊ ግንኙነትን ማረጋገጥ፣ ጤናማ ጉርብትና መፍጠር፣ በጎረቤት ሀገራት ጉዳይ ጣልቃ አለመግባት፣ በሀገራቱ መካከልም ሆነ በሀገራቱ ውስጥ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት፣ ቀጠናቂ ሰላምን መረጋጋት እንዲሁም ደህንነት ማረጋገጥ የኢጋድ ስምምነት ዋንኛ ዓላማዎች ናቸው ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።