ማሻ ፣ የግንቦት 16፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት የካፒታል ፕሮጀክቶች ዕቅድ ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በተገኙበት እየተገመገመ ይገኛል።
በግምገማ መድረኩ ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት ያለዉን ዉስን በጀት በካፒታል ፕሮጀክቶች ላይ በፍትሃዊነት፣በአዋጭነትና ከአስፈላጊነት አኳያ አይቶ በጀት መመደብ ያስፈልጋል ብለዋል።
ከዚህ አኳያ ያለዉን ዉስን ሃብት አስቀድሞ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት ለመጨረስ እንዲሁም ዉጤታማ ስራ ለመስራት የካፒታል ፕሮጀክቶችን የበጀት ፍላጎት መገምገም እንዳስፈለገ ጠቅሰዋል።
ነባር የካፒታል ፕሮጀክቶች እና አዳዲስ የካፒታል ፕሮጀክት በጀት ጥያቄ ያላቸዉ ቢሮዎች ዕቅዳቸዉን እያቀረቡ ይገኛሉ።
ክልል ኮሚኒኬሽን
More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።
የሰው ተኮር ተግባራት በማጠናከር ሁለተናዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገለፁ።