ማሻ ፣ የግንቦት 16፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት የካፒታል ፕሮጀክቶች ዕቅድ ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በተገኙበት እየተገመገመ ይገኛል።
በግምገማ መድረኩ ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት ያለዉን ዉስን በጀት በካፒታል ፕሮጀክቶች ላይ በፍትሃዊነት፣በአዋጭነትና ከአስፈላጊነት አኳያ አይቶ በጀት መመደብ ያስፈልጋል ብለዋል።
ከዚህ አኳያ ያለዉን ዉስን ሃብት አስቀድሞ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት ለመጨረስ እንዲሁም ዉጤታማ ስራ ለመስራት የካፒታል ፕሮጀክቶችን የበጀት ፍላጎት መገምገም እንዳስፈለገ ጠቅሰዋል።
ነባር የካፒታል ፕሮጀክቶች እና አዳዲስ የካፒታል ፕሮጀክት በጀት ጥያቄ ያላቸዉ ቢሮዎች ዕቅዳቸዉን እያቀረቡ ይገኛሉ።
ክልል ኮሚኒኬሽን
More Stories
በህዝቦች መካከል ያለዉን ትስስር ይበልጥ ለማጠናከርና ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ የየአካባቢዉን ባህላዊ የግጭት አፈታት ዜዴ በዘላቂነት ማስቀጠል እንደሚገባ ጥሪ ቀረበ።
አቶ ጌታቸው ረዳ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ በአዲስ አበባ ከሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ጋር በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ውይይት እያደረጉ ነው።
በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት የነጋዴዉ ማህበረሰብ ሚና ጉልህ መሆኑን የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገለጹ።