ሻ ፣ የግንቦት 17፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) 2ኛ ዙር የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያና የጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሰላምና የልማት የትብብር ፎረም በሚዛን አማን ከተማ እተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢጅነር ነጋሽ ዋጌሾ በሁለቱ ህዝቦች መካከል የቆየና የጠበቀ ትስስርና በርካታ መልካም እሴቶች እንዳለ አዉስተዋል ።
በሌላ በኩል በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ በሆኑ አንዳንድ አካባቢዎች አልፎ አልፎ የሚከሰቱት ግጭቶችን በክልሉ ህዝቦች ባህላዊ የግጭት አፈታት ዜዴ የመፍታቱ ተግባር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁሉም በዘላቂነት ትኩረት ሰጥቶ አንዲሰራ አሳስዋል።
የጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ አለምቱ ኡሙድ በበኩላቸዉ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የሁለቱ ክልል ህዝቦች ከዚህ ቀደም በፍቅርና በመተሳሰብ የሚኖሩ መሆናቸዉን አስታዉሰዉ በቀጣይ ለጋራ ሰላምና የልማት ተጠቃሚነት ሁሉም የሚጠበቅበትን እንዲሰራ ጠይቀዋል።
የሰላምና የልማት የትብብር ፎረሙ ላይ የተገኙት የኢፈዲሪ ሰላም ሚንስቴር ሚንስትር አቶ መሐመድ እንድሪስ በበኩላቸው ክልሎቹ በተፈጥሮ ጸጋ የበለጸጉ ከመሆናቸዉም በተጨማሪ ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሰርቶ የሚለወጥበት መሆኑን ተናግረዋል።
ሆኖም ህዝቡን የማይመጥኑ ግጭቶች አልፎ አልፎ ስለሚስተዋሉ በክልሉ ህዝቦች ዉብ የግጭት አፈታት ዜዴ ግጭቶችን መፍታትና መከላከል ላይ ቀጣይነት ባለዉ መልኩ በትኩረት እንዲሠራ ጠይቀዋል።
በመድረኩ የሁለቱ ክልል ህዝቦችን ሰላምናና ልማት በቀጣይነት ልያጠናክሩ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በጋራ በመሚከር የጋራ አቅጣጫ እንደሚቀመጥ ይጠበቃል።
በመድረኩ የፈደራልና የሁለቱ ክልሎች ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የኃይማኖት አባቶች ተሳትፈዋል ።
ዘጋቢ ጌትነት ገረመዉ
More Stories
የ2018 በጀት ዓመት የካፒታል ፕሮጀክቶች የበጀት ዕቅድ እየተገመገመ ነዉ።
አቶ ጌታቸው ረዳ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ በአዲስ አበባ ከሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ጋር በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ውይይት እያደረጉ ነው።
በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት የነጋዴዉ ማህበረሰብ ሚና ጉልህ መሆኑን የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገለጹ።