ማሻ ፣ የግንቦት 15፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የብልጽግና ጉዞና የነጋዴዉ ማህበረሰብ ሚና በሚል መሪ ቃል በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ዞን አቀፍ ምክክር ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ተካሂዷል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ግንባታ ህደት ዉስጥ የነጋዴዉ ማህበረሰብ ሚና ጉልህ መሆኑን ገልጸዋል።
አያይዘዉ ለማንኛዉ ልማት መረጋገጥና ዘላቂ ሰላም አይተከ ሚና ስላለዉ አሁን በዞኑ ያለዉን ሰላም በዘላቂነት ለማስጠበቅ ነጋዴዉ ማህበረሰብ የድርሻዉን አንዲወጣ አሰሳስበዋል።
በመድረኩም በሀገሪቱ ለዉጡን ተከትሎ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን በተመዘገቡ ስኬቶችና ባጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ነጋዴዎችን ለመፍጠር የሚያስችሉና መሰል ጉዳዮች ላይ በሸካ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ተግባሩ አንደሻ የዉይይት መነሻ ሰነድ እየቀረበ ሲሆን ነጋዴዎቹም መክረዉ የጋራ አቅጣጫ እንደሚያስቀሚጡ ይጠበቃል።
ዘጋቢ ጌትነት ገረመዉ
More Stories
የ2017ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት ዝግጅቶች ተጠናቀዋል – የትምህርት ፈተናና ምዘና አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር
የ2017 የፈተና አስተዳደር ስረዓት ዉጤታማ ለማድረግ በየደረጃዉ ያሉ አካላት ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር ይገባቸዋል ተባለ።
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማትና በኮንስትራክሽን በርካታ የሥራ ዕድል እየፈጠረች ነው።