ማሻ ፣ የግንቦት 14፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ሀገሪቱ ያላት የዉሃ ሀብት ከኢትዮጵያ አልፎ ለአጎራባች ሀገራት ተደራሽ እየሆነ መምጣቱን የዉሃና ኢንጂነር ሚኒስቴር ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ተናገሩ።
በዉሃና ሀይድሮ ዲፕሎማሲ ላይ ትኩረት ያደረገ ምክክር በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል።
ሚኒስትሩ በዚህን ወቅት እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ከ1 መቶ 20 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሊትር በላይ የዉሃ ሀብት ቢኖራትም ባላት ሀብት ልክ እየተጠቀመች አይደለም።
በመሆኑም ቀጥሎ ባሉት ጊዜያቶች ያሉትን የዉሃ ሀብቶች በሚገባ በመጠቀም የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ለዚህም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ጨምሮ ባለድርሻ አካላት በትኩረት መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰዋል።
በምክክሩ የፌደራል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ፋና
More Stories
በዘንድሮ ዓመት በሚሰጠዉ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና አጠቃላይ ከሚፈተኑ 19ሺህ በላይ ተማሪዎች ዉስጥ ከ2ሺህ 6መቶ በላይ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተና እንደሚፈተኑ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች
አቶ አንዱአለም ጌታቸው የማሻ ከተማ ከንቲባ ሆነው ተሾሙ፡፡