ማሻ ፣ የግንቦት 14፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ሀገሪቱ ያላት የዉሃ ሀብት ከኢትዮጵያ አልፎ ለአጎራባች ሀገራት ተደራሽ እየሆነ መምጣቱን የዉሃና ኢንጂነር ሚኒስቴር ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ተናገሩ።
በዉሃና ሀይድሮ ዲፕሎማሲ ላይ ትኩረት ያደረገ ምክክር በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል።
ሚኒስትሩ በዚህን ወቅት እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ከ1 መቶ 20 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሊትር በላይ የዉሃ ሀብት ቢኖራትም ባላት ሀብት ልክ እየተጠቀመች አይደለም።
በመሆኑም ቀጥሎ ባሉት ጊዜያቶች ያሉትን የዉሃ ሀብቶች በሚገባ በመጠቀም የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ለዚህም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ጨምሮ ባለድርሻ አካላት በትኩረት መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰዋል።
በምክክሩ የፌደራል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ፋና
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።