ማሻ ፣ የግንቦት 12፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) “በቅርብ ዓመታት ውስጥ፣ ዲጂታል ማንነት ተስፋ ሰጪ ከሆነው ፈጠራ ወደ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን መሠረታዊ ምሦሶ ተሻሽሏል።
ከአሁን በኋላ አማራጭ ሳይሆን ሰዎችን ከአገልግሎቶች፣ ከማኅበረሰቦች፣ ከተቋማት እና ከመንግሥታት ጋር የሚያገናኝ አስፈላጊ መሠረተ ልማት ነው።
ከአምስት ዓመት በፊት በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ራዕይ እየተመራን እጅግ አስፈላጊ ውሳኔ ወስነናል።
ይህም ዘመናዊ፣ አካታች፣ መሠረት ያለው እና ሊሰፋ የሚችል ዲጂታል የማንነት ሥርዓት መገንባት ነው። ይሄንንም ለእያንዳንዱ ነዋሪ ተደራሽ እንዲሆን ማድረግ ነበር።
ይሄንን ሥርዓት ‘ፋይዳ’ ብለን እንጠራዋለን። ፋይዳ ካርድ ብቻ አይደለም። የግለሰቦችን ግላዊ መረጃዎች ምሥጢራዊነት በመጠበቅ እና አስፈላጊ የሆነውን ብቻ በማጋራት ማንነትዎን የሚያረጋግጥ ልዩ መለያ ቁጥር ነው!”
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
More Stories
በተገባደደዉ የበልግ አዝመራ ከ9 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ የእንሰት ችግኝ መትከሉን የአንድራቻ ወረዳ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ፅ/ቤት አስታወቀ ።
አዳዲስ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ወደ ስራ መግባታቸው ለኮንስትራክሽን ዘርፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ተባለ።
መከላከልና አክሞ ማዳንን መሠረት ያደረጉ የጤና ፓሊስዎችን ተግባራዊ በማድረግ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎቶችን መስጠት እንደምገባ የሸካ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገለፁ።