ማሻ ፣ የግንቦት 11፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በስደት፣ መፈናቀል እና ከተማኔነት ላይ ያዘጋጀው 4ኛው የሳይንስ ጉባዔ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
ጉባዔው “ስደት፣ መፈናቀል እና ከተሜነት በዘላቂ ልማት ላይ ያላቸው ተጽዕኖ” በሚል መሪ ሀሳብ ነው እየተካሄደ የሚገኘው።
በመድረኩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን፣ ተመራማሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ከንቲባዎች፣ የልማት ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በጉባዔው የስደትና መፈናቀል ምክንያቶችን በመፈተሽ በእውቀትና ተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሰረቱ የመፍትሄ አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡ ተመላክቷል፡፡
የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን÷ የኢትዮጵያን ውጤታማ የስደተኞች አያያዝ እና አገልግሎት ተሞክሮ አቅርበዋል።
የኢጋድ የኢትዮጵያ ተጠሪ አቶ አበባው ቢሆነኝ በበኩላቸው÷ በቀጣናው የከተማ እድገት ያመጣቸው ፈተናዎች የተቀናጀ እና መረጃን መሰረት ያደረገ ምላሽ እንደሚያሻቸው ገልጸዋል።
ዜጎች በኢጋድ ቀጣና የሚያደርጉት እንቅስቃሴ በከተሞች እድገት፣ ኢኮኖሚ እና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ ጫና እያሳደረ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በቀጣነው የስደተኞችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ ላሉ ሥራዎች ኢጋድ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡
ፋና
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።