ማሻ ፣ የግንቦት 11፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በስደት፣ መፈናቀል እና ከተማኔነት ላይ ያዘጋጀው 4ኛው የሳይንስ ጉባዔ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
ጉባዔው “ስደት፣ መፈናቀል እና ከተሜነት በዘላቂ ልማት ላይ ያላቸው ተጽዕኖ” በሚል መሪ ሀሳብ ነው እየተካሄደ የሚገኘው።
በመድረኩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን፣ ተመራማሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ከንቲባዎች፣ የልማት ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በጉባዔው የስደትና መፈናቀል ምክንያቶችን በመፈተሽ በእውቀትና ተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሰረቱ የመፍትሄ አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡ ተመላክቷል፡፡
የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን÷ የኢትዮጵያን ውጤታማ የስደተኞች አያያዝ እና አገልግሎት ተሞክሮ አቅርበዋል።
የኢጋድ የኢትዮጵያ ተጠሪ አቶ አበባው ቢሆነኝ በበኩላቸው÷ በቀጣናው የከተማ እድገት ያመጣቸው ፈተናዎች የተቀናጀ እና መረጃን መሰረት ያደረገ ምላሽ እንደሚያሻቸው ገልጸዋል።
ዜጎች በኢጋድ ቀጣና የሚያደርጉት እንቅስቃሴ በከተሞች እድገት፣ ኢኮኖሚ እና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ ጫና እያሳደረ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በቀጣነው የስደተኞችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተከናወኑ ላሉ ሥራዎች ኢጋድ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡
ፋና
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።