ማሻ ፣ የግንቦት 06፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ከተረጂነት ወደ ምርታማት በመሸጋገር የተሟላ ሃገራዊ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ከሁሉም የብልጽግና አባላት እንደሚጠበቅ ተገልጿል።
ከተረጂነት ወደ ምርታማት ወደ ተሟላ ሃገራዊ ሉዓላዊነት በሚል መሪ ሀሳብ ቅጽ 1 ቁጥር 6 የልሳነ ብልጽግና ንድፈ ሀሳብ መጽሔት ላይ ከአባላት ጋር ውይይት ተደርጓል።
የመወያያ ሰነዱን ያቀረቡት የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ ከተረጂነት ወደ ምርታማት በመሸጋገር የተሟላ ሃገራዊ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ከሁሉም የብልጽግና አባላት እንደሚጠበቅ አስረድተዋል ።
የክልል ማዕከል አስተዳደር የብልጽግና ህብረት አመራሮችና የብልጽግና ቤተሰብ አባላት በተሳተፉበት በቀረበው የመወያያ ሰነድ ምርታማነትን በማሳደግ የተሟላ ሀገራዊ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ጥገኛ ከሆነ አስተሳሰብ ፈጥኖ መውጣት ይገባል ብለዋል።
በልሳነ ብልጽግና ንድፈ ሀሳብ መጽሔት ሀገራዊ ቁመናን፣ እሳቤያዊና አሁናዊ ሁኔታ እንዲሁም አስቻይ ሁኔታዎች እና ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርምና አንድምታው በተሰኙ ወሳኝ ርዕሶች ላይ ገለጻ አድርገዋል ሲል የክልሉ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።