ማሻ ፣ የግንቦት 03፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ሲካሄድ የቆየው 54ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በድምር ውጤት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
በሻምፒዮናው በድምር ውጤት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ279 ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዞ ሲያጠናቅቅ፣ መቻል በ242 ነጥብ ሁለተኛ እንዲሁም ሸገር ሲቲ በ143 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል።
በሻምፒዮናው 1 ሺህ 379 አትሌቶች፣ 31 ክለቦችና ተቋማት እንዲሁም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተሳትፈዋል።
በሻምፒዮናው ማጠቃለያ ሥነ ሥርዓት ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዲኤታ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህንን ጨምሮ የፌደሬሽኑ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ፋና
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ