ማሻ ፣ የግንቦት 04፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) መምሪያው የኩፍኝ መከላከያ ክትባት ዘመቻን ለማሰጀመር ዓላማ ያደረገ የንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቴፒ ከተማ አካሂዷል ።
የሸካ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ እምሩ ወዬሳ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት የክትባት ዘመቻው ውጤታማ እንድሆን ለዘርፍ ባለሙያዎች ስልጠና ከመስጠት በተጨማሪ አስፈላጊ የሆኑ ግባቶችን የሟሟላት ስራ ተሰርቷል ብለዋል።
ከዘመቻው ጎን ለጎን ህብረተሰቡ ጤናውን እንድጠብቅ የግንዛቤ ስራዎች እንደምሰራ የገለፁት ኃላፊው የክትባት ዘመቻው እንዲሳካ የተሽከርካሪና ሌሎች ድጋፎችን እንደምጠይቅ ገልፀዋል ።
የሸካ ዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊና የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ምንተስኖት እንዳሻው በበኩላቸው የዚህ ክትባት ዘመቻ ዕቅድ እንድሳካ በየደረጃው የምገኙ ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል ።
ለዚህም የዞን አስተዳደር የበኩሉን ድጋፍ እንደምያደርግ ጠቁመው በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች፤ ባለሙያዎች እንድሁም የሀይማኖት አባቶች እና የማህበረሰብ ክፍሎች የበኩላቸውን እንድወጡ አሳስበዋል ።
በዞኑ ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ 48 ሺህ 3መቶ 38 ህጻናት በጤና ተቋማትና ጊዜያዊ የክትባት መስጫ ጣቢያዎች የሚሰጥ ሲሆን የሀይማኖት አባቶችና ለሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ዘመቻው እንዲሳካ አስፈለጊውን ድጋፍ እንድያደርጉ ጥር ቀርቧል።
የመከላከያ ክትባት ዘመቻው ከግንቦት 6 እስከ 15 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ ለተከታታይ 10 ቀናት እንደሚሰጥም ተገልጿል።
ዘጋቢ አስቻለው አየለ
More Stories
የጤና አገልግሎትን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው – ዶ/ር መቅደስ ዳባ
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ከእንግሊዝ መንግሥት የ12 አምቡላንሶች ድጋፍ ተረከበ
የጥርስን ጤና መጠበቅ በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት። የጥርሳችንን ንፅህና መጠበቅ መልካም የአፍ ጠረን እንዲኖረን ከማድረጉ ባለፈ የድድ እና ከአፍ ጋር በተገናኘ የሚፈጠሩ በሽታዎችን እንደሚከላከል የጥርስ ሀኪሞችን አናግሮ ሲኤንኤን ዘግቧል።