May 9, 2025

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በሩሲያ የድል በዓል የአቀባበል ስነ ስርዓት ላይ ተሳተፉ

ማሻ፣ ሚያዝያ 30፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በ80ኛው የሩሲያ የድል በዓል ለሚሳተፉ የሀገራት መሪዎች ማምሻውን በክሬምሊን ቤተ መንግስት በተካሄደው የአቀባበልና የእራት ግብዣ ስነ ስርዓት ላይ ተሳትፈዋል።

የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በድል ቀን በዓል ላይ ለመሳተፍ ለመጡ የሀገራት መሪዎች አቀባበል አድርገዋል።

በስነ-ስርዓቱ ላይ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴን ጨምሮ የተለያዩ የአፍሪካ እና የሌሎች ሀገራት መሪዎች መሳተፋቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

የድል በዓሉ 2ኛው የዓለም ጦርነት ማብቃቱን ተከትሎ በተለይም የቀድሞው ሶቪየት ኅብረት ጦር የተቀዳጀውን ድል በማሰብ በሞስኮ የቀይ አደባባይ የሚካሄደውን ከፍተኛ ወታደራዊ ትርኢት ጨምሮ ሌሎች መርሃ ግብሮች ይከናወናሉ።