ማሻ፣ ሚያዝያ 30፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በ80ኛው የሩሲያ የድል በዓል ለሚሳተፉ የሀገራት መሪዎች ማምሻውን በክሬምሊን ቤተ መንግስት በተካሄደው የአቀባበልና የእራት ግብዣ ስነ ስርዓት ላይ ተሳትፈዋል።
የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በድል ቀን በዓል ላይ ለመሳተፍ ለመጡ የሀገራት መሪዎች አቀባበል አድርገዋል።
በስነ-ስርዓቱ ላይ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴን ጨምሮ የተለያዩ የአፍሪካ እና የሌሎች ሀገራት መሪዎች መሳተፋቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
የድል በዓሉ 2ኛው የዓለም ጦርነት ማብቃቱን ተከትሎ በተለይም የቀድሞው ሶቪየት ኅብረት ጦር የተቀዳጀውን ድል በማሰብ በሞስኮ የቀይ አደባባይ የሚካሄደውን ከፍተኛ ወታደራዊ ትርኢት ጨምሮ ሌሎች መርሃ ግብሮች ይከናወናሉ።
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።