May 9, 2025

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ቼልሲ እና ሪያል ቤቲስ ለዩሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ ፍጻሜ አለፉ

ማሻ፣ ሚያዝያ 30፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) በዩሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታዎች ቼልሲ እና ሪያል ቤቲስ ተጋጣሚዎቻቸውን በመርታት የፍጻሜ ተፋላሚ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡

ምሽት 4 ሰዓት ላይ በስታምፎርድ ብሪጅ የስዊድኑን ዩርጋደን ያስተናገደው ቼልሲ 1 ለ ዐ (በድምር ውጤት 5 ለ 1) በመርታት ለፍጻሜ ማለፍ ችሏል፡፡

በሌላ ጨዋታ ፊዮረንቲና ሪያል ቤቲስን 2 ለ 1 ማሸነፉን ተከትሎ በደርሶ መልስ ውጤት 3 ለ 3 አቻ በመለያየታቸው ሁለቱ ክለቦች ወደ ጭማሪ ደቂቃ አምርተዋል።

በተጨማሪ ደቂቃ ሪያል ቤቲስ ጎል አስቆጥሮ በድምር ውጤት 4 ለ 3 በማሸነፍ የፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል።