ማሻ፣ ሚያዝያ 30፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) በዩሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታዎች ቼልሲ እና ሪያል ቤቲስ ተጋጣሚዎቻቸውን በመርታት የፍጻሜ ተፋላሚ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በስታምፎርድ ብሪጅ የስዊድኑን ዩርጋደን ያስተናገደው ቼልሲ 1 ለ ዐ (በድምር ውጤት 5 ለ 1) በመርታት ለፍጻሜ ማለፍ ችሏል፡፡
በሌላ ጨዋታ ፊዮረንቲና ሪያል ቤቲስን 2 ለ 1 ማሸነፉን ተከትሎ በደርሶ መልስ ውጤት 3 ለ 3 አቻ በመለያየታቸው ሁለቱ ክለቦች ወደ ጭማሪ ደቂቃ አምርተዋል።
በተጨማሪ ደቂቃ ሪያል ቤቲስ ጎል አስቆጥሮ በድምር ውጤት 4 ለ 3 በማሸነፍ የፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል።
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ