ማሻ፣ ሚያዝያ 30፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) በዩሮፓ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድና ቶተንሃም ሆትስፐር ተጋጣሚዎቻቸውን በመርታት የፍጻሜ ተፋላሚ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኦልድትራፎርድ የስፔኑን ክለብ አትሌቲክ ቢልባኦ ያስተናገደው ማንቼስተር ዩናይትድ 4 ለ 1 (በድምር ውጤት 7 ለ 1) በመርታት ለፍጻሜ ማለፍ ችሏል፡፡
የዩናይትድን ግቦች ሜሰን ማውንት (2)፣ ካሴሚሮ እና ራስሙስ ሆይሉንድ አስቆጥረዋል።
ሌላኛው የእንግሊዝ ክለብ ቶተንሃም ሆትስፐር ወደ ኖርዌይ በማቅናት ቦዶ ግሊምትን 2 ለ ዐ (በድምር ውጤት 5 ለ 1) በመርታት የፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል፡፡
ከ2 ሳምንት በኋላ በስፔን ቢልባኦ በሚደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ሻምፒዮን የሚሆነው ክለብ በቀጣዩ አመት የሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡
More Stories
የ2026 የካራባኦ ዋንጫ ፍፃሜ …
ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮንነቷ እንዲሰረዝ መወሰኑ አሳፋሪ ነው፡- የካፍ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ኦጉስቲን ሴንግሆር
ቦርንማውዝ ከ ማንችስተር ዩናይትድ