ሚያዝያ 23፣ 2017 በ27ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና ድሬዳዋ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ዛሬ ረፋድ ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ፥ የኢትዮጵያ ቡናን የማሸነፊያ ግቦች በፍቃዱ አለማየሁ እና አንተነህ ተፈራ አስቆጥረዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና ነጥቡን 42 በማድረስ ወደ 2ኛ ደረጃ ከፍ ሲል፥ ሽንፈት ያስተናገደው ድሬዳዋ ከተማ በ29 ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
በሌሎች የዛሬ መርሐ ግብሮች ቀን 9 ሰዓት ፋሲል ከነማ ከሀዲያ ሆሳዕና እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት መቐለ 70 እንደርታ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ይገናኛሉ፡፡
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ