ማሻ ፣ የመጋቢት 29፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) በ2017/18 የምርት ዘመን ወደ ሀገር ለማስገባት ከታቀደው 24 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እስከ ትናንት ድረስ ከ10 ነጥብ 7 ሚሊየን ኩንታል በላይ ጅቡቲ ወደብ መድረሱ ተገለጸ፡፡
55 ሺህ ሜትሪክ ቶን ዳፕ የአፈር ማዳበሪያ የጫነች መርከብም ጅቡቲ ወደብ ደርሳ ማራገፍ መጀመሯን የማሪታይም ባለስልጣን መረጃ አመላክቷል፡፡
በአጠቃላይ ጅቡቲ ወደብ ከደረሰው ከ10 ነጥብ 7 ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ 9 ነጥብ 6 ሚሊየን ኩንታሉን ወደ ሀገር ውስጥ ማጓጓዝ መቻሉ ተገልጿል፡፡
More Stories
ሚኒስቴሩ ለሦስት ኩባንያዎች የማዕድን ምርት ፍቃድ ሰጠ
በክልሉ ከሚገኙ ቡና አቅራቢ ነጋዴዎች ጋር በወቅታዊ የቡና ገበያ ላይ በቦንጋ ከተማ ምክክር እየተደረገ ነዉ
የጣሊያን ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያላቸውን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲያጠናከሩ ተጠየቀ፡፡