ማሻ ፣ የመጋቢት 08፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን 57ኛው አህጉራዊ የፋይናንስ፣ የኢኮኖሚ ልማትና የፕላን ሚኒስትሮች ጉባዔ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
በጉባዔው ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሐፊ ክላቨር ጋቴቴ፣ የአፍሪካ አሕጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ዋና ጸሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ፣ ሚኒስትሮች፣ የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
ጉባዔው“የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን የሚያፋጥኑ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን መቀየስ”በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተካሄደ የሚገኘው።
የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራ የአፈጻጸም ሒደትና የቀጣይ ተግባራት ላይ በመምከር አቅጣጫ ማስቀመጥ የጉባዔው ዋነኛ አጀንዳ ነው ተብሏል፡፡
ፋና
More Stories
በአዕምሮ የበለጸገ ትውልድ እንዲፈጠር የምግብ -ስርዓትና ስርዓተ – ምግብ ትግበራዎችን በቅንጅት መምራት እንደሚገባ ተገለጸ
267ኛው የሮማ ካቶሊክ ሊቀ ጳጳስ መመረጡን አስመልክቶ በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ የተሰበሰቡ ምዕመናን ደስታቸውን ሲገልፁ
ከባድ የውንብድና እና የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል በእስራት ማስቀጣቱን የሸካ ዞን ፖሊስ አስታወቀ፡፡