ማሻ ፣ የመጋቢት 08፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን 57ኛው አህጉራዊ የፋይናንስ፣ የኢኮኖሚ ልማትና የፕላን ሚኒስትሮች ጉባዔ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
በጉባዔው ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ጸሐፊ ክላቨር ጋቴቴ፣ የአፍሪካ አሕጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ዋና ጸሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ፣ ሚኒስትሮች፣ የአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
ጉባዔው“የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን የሚያፋጥኑ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን መቀየስ”በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተካሄደ የሚገኘው።
የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራ የአፈጻጸም ሒደትና የቀጣይ ተግባራት ላይ በመምከር አቅጣጫ ማስቀመጥ የጉባዔው ዋነኛ አጀንዳ ነው ተብሏል፡፡
ፋና
More Stories
ከባድ የውንብድና እና የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል በእስራት ማስቀጣቱን የሸካ ዞን ፖሊስ አስታወቀ፡፡
በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሙስናን ለመከላከል በተደረገው ጥረት ከ85 ሚሊዮን በላይ ብር የህዝብ ሃብት ማዳን ተችላል
ኢትዮጵያ እና ኢንግሊዝ በኢንቨስትመንት፣ በንግድ እና ኢኮኖሚ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ ተስማሙ