ማሻ ፣ የመጋቢት 04፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በመግለጫቸው የፕሪቶሪያ ስምምነት ተግባራዊ እንዳይሆን ተግዳሮት የሆኑ ጉዳዮችን ለመፍታት መሰራት እንዳለበት አመላክተዋል፡፡
ለክልሉ አላስፈላጊ ገፅታ የሰጡትን ያለፉ ድርጊቶች ማረም ሲገባ በተቃራኒው ሁኔታውን እያባባሱ ያሉ አካላት ከአፍራሽ እንቅስቃሴያቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
ይህ ሕገወጥ እንቅስቃሴ ክልሉን ብቻ ሳይሆን ሀገሪቱን የሚጎዳ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዚህ ሕገወጥ እንቅስቃሴ ምክንያት የክልሉ ነዋሪ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እያለፈ መሆኑን ያነሱት አቶ ጌታቸው፤ ይህም የግጭት አስከፊ ገፅታ ማሳያ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡
የትግራይ ህዝብ ዘላቂ ሰላም ይገባዋል ያሉት አቶ ጌታቸው፤ ከህዝብ ጥያቄ በላይ የስልጣን ጥያቄን የሚያስቀድሙ ግለሰቦች ክልሉን ለባሰ አዘቅት እየዳረጉት ነው ብለዋል።
የፕሪቶሪያ ስምምነት ተፈፃሚነት ከሚገባው በላይ ጊዜ መውሰዱን አንስተው፤ ይህም የክልሉ መረጋጋት የግል ጥቅማችንን ያሳጣናል በሚሉ አካላት ምክንያት የተፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
የፌደራል መንግስት እና የሚመለከታቸው አካላት የጦርነት አማራጭን ለማስቀረት የሚያስችሉ ሁሉንም አስፈላጊ እርምጃዎች እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ኢቢሲ
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።