ማሻ፣ መጋቢት 3፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) ፓትሪስ ሞትሴፔ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዚዳንት ሆነው ለሁለተኛ ጊዜ ያለምንም ተቀናቃኝ ተመርጠዋል።
ደቡብ አፍሪካዊው የ63 ዓመቱ የወቅቱ የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞትሴፔ በድጋሚ መመረጣቸውን ተከትሎ እስከ 2029 ድረስ ካፍን በፕሬዚዳንትነት ይመራሉ።
የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በተገኙበት በዛሬው ዕለት ካይሮ ላይ በተካሄደው የካፍ ልዩ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ፓትሪስ ሞትሴፔ ለተጨማሪ አራት ዓመት የካፍ ፕሬዚዳንት ሆነው እንደሚቆዩ ተረጋግጧል፡፡
ሞትሴፔ ከፈረንጆቹ 2021 ጀምሮ የካፍ ፕሬዚዳንት ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡
ፋና
More Stories
ሲዳማ ቡና የኢትዮጵያ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነ
ቶትነሃም ከ17 አመታት በኃላ ዋንጫ አነሳ፣ የቻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊነቱንም አረጋገጠ
54ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጠናቀቀ