ማሻ፣ መጋቢት 3፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) ፓትሪስ ሞትሴፔ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዚዳንት ሆነው ለሁለተኛ ጊዜ ያለምንም ተቀናቃኝ ተመርጠዋል።
ደቡብ አፍሪካዊው የ63 ዓመቱ የወቅቱ የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞትሴፔ በድጋሚ መመረጣቸውን ተከትሎ እስከ 2029 ድረስ ካፍን በፕሬዚዳንትነት ይመራሉ።
የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በተገኙበት በዛሬው ዕለት ካይሮ ላይ በተካሄደው የካፍ ልዩ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ፓትሪስ ሞትሴፔ ለተጨማሪ አራት ዓመት የካፍ ፕሬዚዳንት ሆነው እንደሚቆዩ ተረጋግጧል፡፡
ሞትሴፔ ከፈረንጆቹ 2021 ጀምሮ የካፍ ፕሬዚዳንት ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡
ፋና
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ