ሻ ፣ የመጋቢት 03 ፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) የ1 ሺህ 446ኛው የሐጅና ዑምራ ጉዞ የምዝገባ ጊዜ እስከ መጋቢት 20 ቀን 2017 ዓ.ም መራዘሙን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስታወቀ፡፡
የተራዘመው የምዝገባ ሒደት ከትናንት ጀምሮ እስከ መጋቢት 20 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ነው የተገለጸው፡፡
ምዝገባው የተሰጠው የጊዜ ገደብ በቂ አለመሆኑ በሕዝበ ሙስሊሙ ዘንድ ጥያቄ መቅረቡን ተከትሎ መራዘሙ ተገልጿል፡፡
ቀኑ የተራዘመው ፍላጎት ያላቸው ሐጃጆችን ለማስተናገድ በማለም መሆኑን የጠቆመው ምክር ቤቱ ÷ ሙስሊሙ ማሕበረሰብ በተሰጠው ጊዜ እንዲመዘገብ ጥሪ አቅርቧል።
ፋና
More Stories
ከባድ የውንብድና እና የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል በእስራት ማስቀጣቱን የሸካ ዞን ፖሊስ አስታወቀ፡፡
በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሙስናን ለመከላከል በተደረገው ጥረት ከ85 ሚሊዮን በላይ ብር የህዝብ ሃብት ማዳን ተችላል
ኢትዮጵያ እና ኢንግሊዝ በኢንቨስትመንት፣ በንግድ እና ኢኮኖሚ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ ተስማሙ