ሻ ፣ የመጋቢት 03 ፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) የ1 ሺህ 446ኛው የሐጅና ዑምራ ጉዞ የምዝገባ ጊዜ እስከ መጋቢት 20 ቀን 2017 ዓ.ም መራዘሙን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስታወቀ፡፡
የተራዘመው የምዝገባ ሒደት ከትናንት ጀምሮ እስከ መጋቢት 20 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ነው የተገለጸው፡፡
ምዝገባው የተሰጠው የጊዜ ገደብ በቂ አለመሆኑ በሕዝበ ሙስሊሙ ዘንድ ጥያቄ መቅረቡን ተከትሎ መራዘሙ ተገልጿል፡፡
ቀኑ የተራዘመው ፍላጎት ያላቸው ሐጃጆችን ለማስተናገድ በማለም መሆኑን የጠቆመው ምክር ቤቱ ÷ ሙስሊሙ ማሕበረሰብ በተሰጠው ጊዜ እንዲመዘገብ ጥሪ አቅርቧል።
ፋና
More Stories
በመስክ ምልከታው የተገኘው ልምድ የሌማት ትሩፋት አካል በመሆኑ አርሶ አደሮቻችንን ተጠቃሚ ለማድረግ ተጠናክሮ ሊሰራ ይገባል፦
የኢራን አዲሱ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ …
የኢትዮጵያ የቀይ ባሕር ባለቤትነት ጥያቄ ለቀጣናዊ ሰላም ያለው ፋይዳ