ማሻ ፣ የመጋቢት 03 ፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) የሸካ ዞን ሴቶች፣ህፃናት፣ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት ተግባር አፈፃፀም እና የቀጣይ አቅጣጫ ላይ የምክክር መድረክ በማሻ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
መድረኩን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የሸካ ዞን ሴቶች፣ህፃናት፣ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ትዕግስት ከበደ እንደገለፁት በዞኑ የፆታ እኩልነትን በማረጋገጥ የሚታዩ ክፍተቶችን በማረም ውጤታማ ለውጥ ማስመዝገብ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የመወያያ ሰነድ ያቀረቡት የየመዋቅሩ ኃላፊዎች እንደገለፁት የሴቶችንና ህፃናት መብትና ደህንነት ማስጠበቅ መቻሉን፣የወጣቶች ማካተት ንቅናቄና ተሳትፎና ለሎች ተግባራት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱ በጠንካራ ጎን አንስተዋል ።
በአስተዳደር ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት ማነስ፣የሴቶች ንቅናቄና ተሳትፎ ስራ ዝቅተኛ መሆን፣የሴቶች የመሬት ባለቤትነት መረጃ የተጋነነ መሆን፣የስራ አጥ ወጣት ልየታ ያለመደረግና የመሳሰሉት አጀንጃዎች ላይ የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ምክክር እየተደረገ ነው።
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ