ማሻ ፣ የመጋቢት 03 ፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) ኢትዮጵያ ለንግድና ኢንቨስትመንት መጎልበት በትኩረት እየሰራች ነው ሲሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም ኤምባሲ የልማት ዳይሬክተር ፖል ዋልተርስ የተመራን ቡድንን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ኢትዮጵያ ለንግድና ኢንቨስትመንት መጎልበት በትኩረት እየሰራች መሆኗንና ከመቼውም ጊዜ በላይ አስቻይ ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበናል ሲሉ ለልኡካን ቡድኑ መግለጻቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡
ኢትዮጵያና ዩናይትድ ኪንግደም ጠንካራ የንግድ ግንኑነት ያላቸው ሀገራት ናቸው ያሉት ሚኒስትሩ ሚስተር ፓል በበኩላቸው ዩናይትድ ኪንግደም ኢትዮጵያ እያሳየች ላለችው የኢኮኖሚ ሪፎርም ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል ሲሉም ገልጸዋል።
ለአለም ንግድ ድርጅት አባልነት እያደረግን ያለውን ዝግጅትም አድንቀዋል ብለዋል፡፡
በሁለትዮሽ የገበያ ዕድሎች ዙሪያ በቀጣይነት በጋራ በምንሰራባቸው አግባቦች ላይ ውጤታማ ውይይት አድርገናል ሲሉም ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
ኢዜአ
More Stories
ሚኒስቴሩ ለሦስት ኩባንያዎች የማዕድን ምርት ፍቃድ ሰጠ
በክልሉ ከሚገኙ ቡና አቅራቢ ነጋዴዎች ጋር በወቅታዊ የቡና ገበያ ላይ በቦንጋ ከተማ ምክክር እየተደረገ ነዉ
የጣሊያን ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያላቸውን የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲያጠናከሩ ተጠየቀ፡፡