ማሻ ፣ የመጋቢት 03 ፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም ) የማጠቃለያ መድረኩን የመሩት የሸካ ዞን ግብርና መምረያ ሀላፍ አቶ አዕምሮ ደሳልኝ እና የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ መስፍን አዳሾ እንደገለፁት የግብርና ባለሙያዎች አገልግሎት መቀዛቀዝ በግብርና ተግባር ላይ ያሳደረውን አሉታዊ ተፅዕኖን ለመቅረፍ ያስፈልጋል ብለዋል።
በዚህም የቴክኖሎጂ አጠቃቀማችንን በማሻሻል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በሀገር ደረጃ የታየውን የኑሮ ውድነት ለመቅረፍ መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል ።
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ መስፍን አዳሾ እንደገለፁት በየዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች የሙያውን መብትና ግደታ በመረዳት ከዚህ በኋላ ባለው ጊዜ በግምገማው የተቀመጡ አቅጣጫዎችንና ትምህርቶችን ተግባራዊ በማድረግ የተሻለ አፈጻጸም ማሳየት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
የግምገማው ውጤት በተመለከተም አጠቃላይ የተገመገሙ ወንድ 67 ሴት 52 በድምሩ 119,የተገመገሙ ሲሆን በማስጠንቀቂያ ወንድ 15 ሴት 10 በድምሩ 25 እና በዲስፕሊን ወንድ 1 እንዲሁም ፤ በህስ ወንድ 51 ሴት 42 በድምሩ 93 ባለሙያዎች እንዲጠየቁ ውሳኔ የተወሰነ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል።
በመድረኩም የግብርና ባለሙያዎች ችግር ፈች ድጋፍ ያለማድረግ፣ የኤፍቲስ ማሳዎችን ሞዴል ያለማድረግ ፤ ዉሎአድሮ በቦታው ተተክሎ አለመስራት ፤ የግባዓት አቅረቦ ችግር ፤ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዝቅተኛ መሆን ፤ የሕግ-ወጥ መሬት ወረራን ያለመከላከል ፣ በክህሎትና በባለሙያ የሥራ ሥነ-ምግባር ችግር እንዲሁም በማስፈጸም ረገድ የሚታዩ ውስንነቶች በግምገማ ላይ በሰፊው ተነስቷል።
በመድረኩም የክልል ፣ የዞንና የወረዳ አጠቃላይ አመራሮች ጨምሮ የ19ኙ ቀበሌ አስተዳዳሪዎችና የፓይለት አመራሮች እንዲሁም የግብርና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
ወረዳ ኮሚኒኬሽን
More Stories
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።
የሰው ተኮር ተግባራት በማጠናከር ሁለተናዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገለፁ።
የህዳሴው ግድብ መጠናቀቅ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስርን ያሳድጋል